የ አዲስ ሽማግሌዎች የሹመት እና የቀድሞ ሽማግሌዎች የሽኝት ፕሮግራም
እ.ኤ.አ. ግንቦት (Mai) 17 ቀን 2026 (17.05.2026) በቤተክርስቲያናችን ውስጥ እጅግ በጣም አነቃቂ እና ደስ የሚል ፕሮግራም አሳልፈናል። በዚህ በዓል ላይ አዳዲስ የቤተክርስቲያን ሽማግሌዎች በይፋ ተሾመው እና ተባርከዋል።
ለ8 ዓመታት ታማኝ አገልግሎት ምስጋና
ከስምንት ዓመታት የቁርጠኝነት አመራር አገልግሎት በኋላ ሁለቱ የቀደሙት ሽማግሌዎቻችን ከኃላፊነታቸው በክብር ተሰናብተዋል። ቤተክርስቲያናችንን በተለያዩ ደረጃዎች በእውቀት፣ በፍቅር እና በትጋት መርተዋል። በዚህ ፕሮግራም ላይ ለረጅም ዓመታት ላደረጉት አስተዋጽኦ ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን፤ ለቀጣይ መንገዳቸውም የእግዚአብሔርን በረከት እና ጸጋውን እንዲያበዛላቸው እንመኛለን!
አዲስ ጥሪ እና ሹመት
በዚሁ ፕሮግራም ላይ ሁለት አዳዲስ ሽማግሌዎችን በይፋ ወደ አመራር አስተዋውቀናል:: ከፓስተራችን እና ከቀሩት ሁለት ሽማግሌዎች ጋር በመሆን ከአሁን ጀምሮ የቤተክርስቲያናችንን መንፈሳዊ እና አስተዳደራዊ አመራር ይረከባሉ።
የአመራር ቡድኑ እንደሚከተለው ነው፡
- ፓስተር (Pastor): መጋቢ እሸቱ ጉርሙ
- የሽማግልና ኃላፊነታቸውን የሚቀጥሉ (Weiterhin im Amt): በለጠ ብርሃኑ እና ከበደ ጥላሁን
- አዲስ የተሾሙ (Neu ordiniert): ሰለሞን ነጋ, ሰለሞን ጥላሁን
- የተሸኙ ሽማግሌዎች (Verabschiedete Älteste): ዘላለም አስፋው እና ክንፈ ብርሃኑ
በዚህ አዲስ ጅምር እና አዲስ እይታ ጌታ ለቤተክርስቲያናችን ስላዘጋጀ በጣም ደስተኛ ነን። እባካችሁ ሙሉውን የአመራር ቡድን በጸሎት እና በድጋፍ አስቡአቸው።
Feierliche Ordination in der Gemeindeleitung
Am vergangenen 17. Mai 2026 erlebten wir in unserer Gemeinde ein besonders bewegendes Programm: Im Rahmen einer festlichen Ordination wurden neue Älteste offiziell in ihren Dienst eingesetzt und gesegnet.
Dank und Würdigung für 8 Jahre treuen Dienst
Nach acht Jahren engagierter Leitung traten zwei unserer bisherigen Ältesten aus dem Amt zurück. Mit viel Herzblut, Weisheit und persönlichem Einsatz haben sie unsere Gemeinde durch unterschiedlichste Phasen geprägt. Im Rahmen dieses Programms durften wir ihnen für ihren jahrelangen Einsatz unseren tiefen Dank aussprechen. Wir wünschen ihnen für ihren weiteren Weg Gottes reichen Segen!
Neue Berufung und Beauftragung
Gleichzeitig durften wir bei diesem Programm zwei neue Älteste durch Ordination feierlich in ihr Amt einführen. Gemeinsam mit unserem Pastor und den zwei verbleibenden Ältesten übernehmen sie ab sofort die geistliche und organisatorische Leitung unserer Gemeinde.
Das Leitungsteam setzt sich wie folgt zusammen:
- Pastor: Pastor Dr. Eshetu Gurmu
- Weiterhin im Amt: Belete Birehanu, Kebede Tilahun
- Neu ordiniert: Solomon Nega, Solomon Tilahun
- Verabschiedete Älteste: Kinfe Birehanu und Zelalem Asfaw
Wir freuen uns über diesen Schritt, die frischen Impulse und den gemeinsamen Weg. Bitte begleitet das gesamte Leitungsteam weiterhin mit eurem Gebet und eurer Unterstützung.







የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን Frankfurt 36 ዓመታት ጉዞ፡ የቤተክርስቲያን ታሪክ
ውድ የቤተክርስቲያናችን አባላት እና ወዳጆች፡
መጋቢ ፓስተር እሸቱ ጉርሙ ነኝ። በፍራንክፈርት የምትገኘው የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ከተመሠረተች አሁን ፫፮ ዓመታትን አስቆጥራለች። እኔ ገና ከመጀመሪያው ጀምሮ የዚሁ ህብረት አባል የነበርኩ ከዛም በመቀጠል የቤተክርስቲያኗ ፓስተር በመሆን ኣሁንም እያገለገልኩ ነው።
በነዚህ ዓመታት ውስጥ ያየናቸውን ውጣ ውረዶች፣ የተማርናቸውን ትምህርቶች እና የቤተክርስቲያናችንን ታሪክ የሚያታውስ መጽሐፍ ጽፌ ጌታ ረድቶኝ አዘጋጅቻለሁ። ስለ ቤተክርስቲያናችን ታሪክ እና አመሠራረት በሰፊው ማወቅ ለሚፈልጉ የቤተክርስቲያናችን አባላት እና ወዳጆች በሙሉ መጽሐፉ ዝግጁ ሆኖ ይገኛል።
ስለ መጽሐፉ ሽያጭ፡
መጽሐፉን በቤተክርስቲያናችን በመገኘት መግዛት ይችላሉ። ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በሙሉ ለቤተክርስቲያናችን አገልግሎት የሚውል ነው።
Einblicke in 36 Jahre Äthiopische Gemeinde in Frankfurt: Unser gemeinsamer Weg
Liebe Gemeinde, liebe Leserinnen und Leser,
ich heiße Pastor Dr. Eshetu Gurmu . Seit 36 Jahren gibt es unsere Äthiopische Evangelische Gemeinde hier in Frankfurt. Ich war von den ersten Tagen an Teil dieser Gemeinschaft und habe ihren Weg über die Jahrzehnte hinweg persönlich begleitet – später habe ich schließlich das Amt des Pastors übernommen.
In meinem Buch habe ich all die Erlebnisse, Höhen und Tiefen sowie die Erkenntnisse aus all diesen Jahren niedergeschrieben. Es steht allen Mitgliedern und Interessierten zur Verfügung, die mehr über die Geschichte, die Anfänge und die Entwicklung unserer Gemeinde erfahren möchten.
Wichtiger Hinweis: Das Buch ist direkt bei uns in der Gemeinde erhältlich. Alle Einnahmen aus dem Verkauf fließen als Spende zu 100 % in die Arbeit unserer Gemeinde.






